የሀገር ውስጥ ዜና

በሩብ ዓመቱ 73 ቢሊየን ብር ገቢ ተሰብስቧል

By Feven Bishaw

November 29, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 20 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 ዓ.ም ሩብ ዓመት 73 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ሰላማዊት ካሳ በ2014 ዓ.ም 407 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውሰው በሩብ ዓመቱ 73 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡