የሀገር ውስጥ ዜና

ቦርዱ በመራጮች ትምህርትና መረጃ አሰጣጥ ዙሪያ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ምክክር አካሄደ

By Tibebu Kebede

February 13, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርት እና መረጃ አሰጣጥን አስመልክቶ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ምክክር አካሂዷል።

ቦርዱ የመገናኛ ብዙሃን ተደራሽነት እና ሚና ለመራጮች ትምህርት በሚል ርዕስ ነው የምክክር መድረኩን በዛሬው እለት ያካሄደው።