የሀገር ውስጥ ዜና

በአፍሪካ ቀንድ የአርብቶ አደሮችን ስርአተ ምግብ ለማሻሻል ያለመ የፓናል ውይይት ተካሄደ

By Feven Bishaw

November 29, 2021

 

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 20 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለሶስተኛ ጊዜ በአፍሪካ ቀንድ የሚገኙ አርብቶ አደሮችን ስርአተ ምግብ ለማሻሻል ያለመ የፓናል ውይይት በጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት በዛሬው እለት ተካሂዷል፡፡

በፓናል ውይይቱ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅቶችን ጨምሮ በሶማሌ ክልል የሚገኙ ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች የተሳተፉ ሲሆን፥ ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ ተመላክቷል ።