የሀገር ውስጥ ዜና

የተለያዩ ተቋማት ለህልውና ዘመቻ ከ18 ሚሊየን ብር በላይ ደጋፍ አደረጉ

By ዮሐንስ ደርበው

December 01, 2021

በሌላ በኩል የጅማ ዞን የማና ወረዳ ቄሮና ቀሬዎች 4 ሚሊየን ብርና 66 በሬዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አድርገዋል።

ከድጋፉ በተጨማሪ የወረዳው ቄሮዎች፥ የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይን ዱካ በመከተል መከላከያ ሰራዊትን ለመቀላቀል መመዝገባቸው ተገልጿል።

ወጣቶቹ “ከዚህ ቀደም መንገድ ዘግተን ወያኔን ከስልጣን እንዳስወገድነው ሁሉ፥ አሁንም ከወረረው መሬት ንብረት ዘርፎ እንዳይወጣ ግብዓተ መረቱትን እንደሚፈፅማለን” ብለዋል።

የማና ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ፈድሉ ዛኪር፥ መከላከያን ለመደገፍ የወረዳው ወጣቶች ጋ ያለው ተነሳሽነት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፥ በርካታ ወጣቶች ግንባር ድረስ ለመዝመት ፍላጎት ማሳየታቸውን ገልፀዋል።

በድጋፍ ስነስርአቱ ላይ የተገኙት የጅማ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ የሱፍ ሻሮ በበኩላቸው፥ በአጠቃላይ የዞኑ ነዋሪዎች ለሰራዊቱ 136 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውንና የወጣቶች አስተዋፆም ከፍተኛ መሆኑን ተናግሯል።

በሙክታር ጠሃ