የሀገር ውስጥ ዜና

በቀጣዮቹ ቀናት ከካራቆሬ እስከ ከሚሴ ያለው የኤሌክትሪክ መስመር የመጠገን ሥራ ይከናወናል

By Feven Bishaw

December 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ህዳር 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀጣዮቹ ቀናት ከካራቆሬ እስከ ከሚሴ ያለው የኤሌክትሪክ መስመር የመጠገን ሥራ እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡

እንዲሁም በሽብርተኛው ህወሃት ቡድን ጉዳት የደረሰባቸው ከሸዋ ሮቢት እስከ ካራቆሬ ባሉት ከተሞች የሚገኙ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተጠግነው መጠናቀቃቸው ተገልጿል፡፡