የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ተጨማሪ 500 ሚሊየን ብር ለሪቮልቪንግ ፈንድ ፈቀደ

By Feven Bishaw

December 07, 2021

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የመሰረታዊ ፍጆታ ምርት ለማቅረብ እና የእሕል የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ከዚህ ቀደም ካደረገው ብድር በተጨማሪ የ500 ሚሊየን ብር ለሪቮልቪንግ ፈንድ ፈቀደ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ሕዳር 20 ቀን 2014 ዓ.ም በአንደኛ ዓመት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡