አዲስ አበባ፣ ህዳር 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከካራቆሬ – ከሚሴ ያለው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ከሥርጭት ኔትወርክ መስመሮች ጋር እንዲገናኙ ለማድረግ በርብርብ ሲሰራ ቆይቶ ነው ዛሬ እስከ ከሚሴ ድረስ ያሉት ከተሞች ኃይል ማግኘት የቻሉት፡፡