አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀናጀ የሚዲያና የአንዳንድ መንግስታትን የሀሰት ትርክት ውርጅብኝ በኢትዮጵያውያን ትግል ተቋቁመናል ሲሉ በእንግሊዝ የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ ተናግረዋል፡፡
አምባሳደሩ ይሄንን ያሉት÷ ‘ኢትዮጵያን እናድን’ በሚል መሪ ቃል በአማራና አፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ የሚውል ገቢ ለማሰባሰብ በተዘጋጀ መርሃ ግብር ላይ ከ370 ሺህ ፓውንድ በላይ ማሰባሰብ መቻሉ በተገለጸበት ወቅት ነው፡፡