የሀገር ውስጥ ዜና

ሦስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት የ72 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

December 15, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሦስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት የ72 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል የሱፍ ዩኒቨርሲቲው 15 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን ጠቅሰው፥ “አገርና ትውልድን የማስቀጠል ሃላፊነት በሚገባ በመገንዘብ ዛሬም ለጀግኖቻችን ድጋፍ በማድረጋችን ታላቅ ኩራት ተሰምቶናል” ብለዋል፡፡