አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጌዴኦ ዞን ነዋሪዎች ከ6 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር በላይ በገንዘብ የሚተመን ቁሳቁስ በአፋርና አማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ነው ድጋፍ ያደረጉት፡፡
ኢትዮጵያዊነት ማለት በደስታም ሆነ በሀዘን መረዳዳትና ያለን ተካፍሎ መኖር ነውና ወገኖቻችን በሜዳ ላይ ተበትነው የሚለብሱት የሚቀምሱት ሳይኖራቸው አይቶ ዝም የሚል አንጀት የለንም ካለን ላይ ብቻ ሳይሆን ያለንን አካፍለን እንለግሳለን፤ እኛ እያለን አይቸገሩም በማለት የተለያዩ ቁሳቁስ ለግሰዋል፡፡