አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ወረራውን ለመቀልበስ የፈጠርነውን ሀገራዊ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላምና ለሃገር ግንባታ ልንጠቀምበት ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡
ከንቲባዋ “ከጦርነት ወደ ብልፅግና በሰላም ጎዳና” በሚል መሪ ቃል በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ከመዲናዋ አመራሮች፣ ከክፍለ ከተሞች ተቋማት፣ ከመንግስትና ከግል ሚዲያ አመራሮችና ከኪነጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም መምህራን ጋር ተወያይተዋል፡፡