የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በድርቅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች 70 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

December 17, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በድርቅ ለተጎዱ የህብረተሰብ ክፍሎች 70 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

3ኛው የህብረት ስራ ማህበራት ቀን በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ አዘጋጅነት የህብረት ስራ ማህበራት ለተሻለ ኢኮኖሚ በሚል መሪ ቃል በአዳማ ገልማ አባገዳ ተካሄዷል፡፡