የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ከምንጊዜውም በላይ የህዝቧን አንድ መሆን እና ተባብሮ መስራትን የምትፈልግበት ጊዜ ላይ ናት – ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ

By Feven Bishaw

December 17, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አንጎላ የተገኙት ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በአንጎላ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከምንጊዜውም በላይ የህዝቧን አንድ መሆን እና ተባብሮ መስራትን የምትፈልግበት ጊዜ ላይ ናት ያሉት ፕሬዚዳንቷ ኢትዮጵያውያኑ አንድነታቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል፡፡