አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከውጭ የሚገባውን ስንዴ ለማስቀረትና በምርት እንደሀገር ራስን ለመቻል ባለፉት ሶስት ዓመታት መንግስት ስንዴን በስፋት ለማምረት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር መለስ መኮንን ተናግረዋል።
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅና ምዕራብ ደንቢያ በክላስተር ስንዴን በመስኖ የማልማት ስራ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተጀምሯል።