የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገራችን ያጋጠማትን ችግር ያለማንም ጣልቃ ገብነት እኛው እየፈታን እንገኛለን-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

December 19, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገራችን ያጋጠማትን ችግር ያለማንም ጣልቃ ገብነት እኛው አንድ በመሆን መፍታት እንችላለን፤ እየፈታንም እንገኛለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡

“እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ፣ ሰላም ይስፈን፣ በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚደርስ ጥቃት ይቁም” በሚል መሪ ቃል አሸባሪው ህወሓት በሴቶች እና ህጻናት ላይ የፈጸመውን ጥቃትና አስገድዶ መድፈር የሚያወግዝ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ተካሄደ።