የሀገር ውስጥ ዜና

ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመቆም ለቀጣናው ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገውን ጥረት መደገፍ አለብን -የአሜሪካ ኮንግረስ አባሏ ሼይላ ጃክሰን ሊ

By Feven Bishaw

December 19, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከከፋፋይ ኃይሎች በተቃራኒው ተሰልፈን ከኢትዮጵያ ጋር በመቆም አሁን ያለው መንግሥት ለሀገሪቱ ሕዝቦች እና ለቀጣናው ሀገራት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገውን ጥረት መደገፍ ይገባል ሲሉ የአሜሪካ ኮንግረስ አባሏ ሼይላ ጃክሰን ሊ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር ጠንካራ የኢኮኖሚ ሞተር ነች ያሉት የኮንግረስ አባሏ፥ በከፋፋይ ሃይሎች ሴራ ሳንዘናጋ ከኢትዮጵያ ጋር በመቆም መንግስት ለሀገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የሚያደርገውን ጥረት መደገፍ አለብን ብለዋል በቲዊተር ገጻቸው ላይ።