አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የእስራኤል መንግስትና ህዝብ በግጭቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች 14 ቶን የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡
የእስራኤል መንግስት በአሸባሪውና ወራሪው ህወሓት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቀለው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎችና በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን ግምቱ 14 ቶን የሆነ የንጽህና መጠበቂያ፣ ክራንች፣ ዊልቼርና የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ለሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስርክቧል፡፡