አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “መላ ኢትዮጵያውያን እያደረጉት ያለው ሁለንተናዊ ድጋፍ በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ጉዳት የደረሰበት ህዝባችንን ለማቋቋም የሚያስችል ነው” ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ገለጹ።
የፍትህ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ጠበቆችና የሕግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በመተባበር የ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር እና የአይነት ድጋፍ ለአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት አስረክበዋል።