አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 13 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሳምንታት በተካሄደው “ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚመራው ጥምር የወገን ጦር በአሸባሪው ህወሃት ላይ በወሰደው እርምጃ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ መድረሱን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒሰትር ዲኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ይህን ሽንፈቱን ለመደበቅም ብዙ ርቀት ሂዷል ያሉት ሚኒስትር ዴኢታው በተለይም የሽብር ቡዱኑ “ታጣቂዎቻችንን ከአማራ እና ከአፋር ክልል እንዲወጡ አድርገናል” የሚል ትርክት እያራገበ ነው ብለዋል፡፡
የውሸት ትርክቱም የዓለምን ህዝብ ለማሳሳት፣ የትግራይ ህዝብን ለማታለልና ልጆቹን ለተጨማሪ ጦርነት እንዲያዘጋጁ ለማድረግ የተደረገ ነው ብለዋል፡፡
በአሁኑ ጊዜም የሽብር ቡድኑ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከአማራና አፋር ክልሎች እየፈረጠጠ ነው ብለዋል አቶ ከበደ፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊቱም የሽብር ቡድኑ ዳግም ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ስጋት እንዳይሆን አስፈላጊውን ርምጃ መውሰዱን ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!