አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋና ዋና ሀገራዊ እና የሀገረ መንግሥት ግንባታን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ምክክሮች እንደሚያስልጉ መንግሥት በጽኑ እንደሚያምን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ ምክክሩ በአንድ ጊዜ ተጀምሮ የሚጠናቀቅ ባለመሆኑ፥ ምክክሩን ለማስጀመር ተቋማዊና ህጋዊ ማዕቀፎችን የማዘጋጀት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡