የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ከ313 ሺህ በላይ ተፈናቃይ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል

By Feven Bishaw

December 24, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው የህወሃት ወራሪ ቡድን ከተፈናቀሉት ውስጥ እስካሁን ከ313 ሺህ በላይ ወገኖች ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያሱ መስፍን ቡድኑ በወረራ በቆየባቸው አካበቢዎችም ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን የሚበልጥ ህዝብ ከቤት ንብረቱ በማፈናቀል ለከፋ ችግር እንዲጋለጥ ማድረጉን አስረድተዋል።