አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው የህወሃት ወራሪ ቡድን ከተፈናቀሉት ውስጥ እስካሁን ከ313 ሺህ በላይ ወገኖች ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያሱ መስፍን ቡድኑ በወረራ በቆየባቸው አካበቢዎችም ከ2 ነጥብ 3 ሚሊየን የሚበልጥ ህዝብ ከቤት ንብረቱ በማፈናቀል ለከፋ ችግር እንዲጋለጥ ማድረጉን አስረድተዋል።