የሀገር ውስጥ ዜና

በደሴ ከተማ በሚገኘው የሰይድ ያሲን የንግድ ማእከል እና ድርጅቶች በአሸባሪው ህወሃት መዘረፋቸው ተገለጸ

By Feven Bishaw

December 25, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በደሴ ከተማ በሚገኘው የሰይድ ያሲን የንግድ ማእከል ውስጥ ይሰሩ የነበሩ 113 ድርጅቶች በአሸባሪው ቡድን መዘረፋቸው ተገለጸ።

አሸባሪው ቡድን ከዘረፈው የሕዝብ ሀብት በተጨማሪ በህንጻው ውስጥ የነበረውን ሀብት በመሰባበር እና በተለያዩ መልኮች ከጥቅም ውጭ አድርጓል።