አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ ከጤና ማህበራዊ ልማት ፣ ከባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና አባላት እንዲሁም ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት አድርጓል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በውይይቱ ላይ ፥ አሁን ባለው መዘናጋት ምክንያት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋና በየጊዜው እራሱን እየቀያየረ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ እያደረሰ ነው ብለዋል።