የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአስከፊ ሁኔታ እየተሰፋፋ ስለመጣ ሁሉም ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል ተባለ

By Feven Bishaw

December 25, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ ከጤና ማህበራዊ ልማት ፣ ከባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢና አባላት እንዲሁም ከሌሎች የስራ ኃላፊዎች ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት አድርጓል።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በውይይቱ ላይ ፥ አሁን ባለው መዘናጋት ምክንያት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋና በየጊዜው እራሱን እየቀያየረ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ እያደረሰ ነው ብለዋል።