አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የሎጀስቲክስ ዋና መምሪያን ህንፃ አስመረቀ።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስተዳደር ልማት ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ነቢዩ ዳኜ፥ የተመረቀው የሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ህንፃ በፌደራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ የእድገት ምልክት ሆኖ የሚያገለግል፣ የሪፎርማችን ውጤት የሆነና ለሠራዊቱ ትልቅ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል፡፡