አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በ33ኛው የካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ያዘጋጀው ይፋዊ የሽኝት መርሐ ግብር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል።
በፕሮግራሙ ላይ በቪዲዮ የተቀረፀ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ብሄራዊ ቡድኑ በካሜሩን የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግብ ተመኝተዋል።