የሀገር ውስጥ ዜና

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ

By Feven Bishaw

December 27, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ፋግታ ለኮማ ወረዳ በአሸዋ ቀበሌ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በ3 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።

አደጋው ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከቲሊሊ ወደ ባህር ዳር ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን ከዳንግላ ወደ አዲስ ቅዳም ሲጓዝ ከነበረ የጭነት አይሱዚ መኪና ጋር በመጋጨቱ የደረሰ ነው፡፡