አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካ ስራ መጀመሩ ተገለፀ፡፡
ዋይ ቢ ኤም የተሰኘው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካው በ104 ሚሊየን ብር በይርጋለም ግብርና ማቀነባበርያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተቋቋመና የአቮካዶ ዘይት በማምረት ወደ ውጭ የሚልክ ነው፡፡
በይርጋለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ3ዓመት በፊት ስራ የጀመረው ሌላኛው ” ሳንቫዶ ” የተሰኘው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካ ከ88 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠርና ምርቱን በመሰብሰብ ለግብዓትነት ተጠቅሞ ያመረተውን የዘይት ምርት ወደ ኔዘርላንድ እየላከ ይገኛል፡፡