የሀገር ውስጥ ዜና

ሁለተኛው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካ ስራ ጀመረ

By Feven Bishaw

December 30, 2021

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካ ስራ መጀመሩ ተገለፀ፡፡

ዋይ ቢ ኤም የተሰኘው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካው በ104 ሚሊየን ብር በይርጋለም ግብርና ማቀነባበርያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የተቋቋመና የአቮካዶ ዘይት በማምረት ወደ ውጭ የሚልክ ነው፡፡

 

በይርጋለም አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ3ዓመት በፊት ስራ የጀመረው ሌላኛው ” ሳንቫዶ ” የተሰኘው የአቮካዶ ዘይት ፋብሪካ ከ88 ሺህ አርሶ አደሮች ጋር ትስስር በመፍጠርና ምርቱን በመሰብሰብ ለግብዓትነት ተጠቅሞ ያመረተውን የዘይት ምርት ወደ ኔዘርላንድ እየላከ ይገኛል፡፡