ዓለምአቀፋዊ ዜና

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአዲሱ አመት ጉዟቸው አፍሪካን ይጎበኛሉ

By Feven Bishaw

December 30, 2021

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ በፈረንጆቹ አዲስ አመት የመጀመሪያ ጉዟቸው አፍሪካን እንደሚጎበኙ አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሩ ከፈረንጆቹ ጥር 4 እስከ 7 በኤርትራ፣ ኬንያ እና ኮሞሮስ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ዣኦ ሌጂያን ገልጸዋል፡፡