የሀገር ውስጥ ዜና

የጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ አገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት ጀመሩ

By Feven Bishaw

December 30, 2021

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ አገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት ጀምረዋል።

ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት አራት ቀናት የሚቆየው ውይይት ፥ የተገኙትን ሁለንተናዊ ድሎች ጠብቆ የማስፋትና ወደ ዘላቂ ሰላምና ልማት ማሸጋገር ላይ ያተኮረ ይሆናል ተብሏል፡፡