የሀገር ውስጥ ዜና

የተመዘገበውን አገራዊ ድል አስጠብቆ መዝለቅ ይገባል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

By Feven Bishaw

January 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በድህረ ጦርነት ድላችንን አስጠብቆ መዝለቅ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ  አቶ መለሰ አለሙ የተገኘውን አገራዊ ድል ዘላቂ በማድረግ ብልፅግናን እውን ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ጋር ተወያይተዋል፡፡