አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለክርስትና እምነት ተከታዮች የገና በዓልን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
በመልዕክቱም የገና በዓል የእምነቱ ተከታዮች የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክሩበት፣ መንፈሳዊ እሴቶቻቸውን የሚያዳብሩበት፣ ተቻችለውና ተከባብረው በጋራ መኖርንና መስራትን ለመላው የዓለም ህዝብ የሚያሳዩበት ታላቅ በዓል መሆኑን አውስቷል፡፡