አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2014 ( ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት÷ ለእምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሰላም እና የደስታ እንዲሆን የተመኙ ሲሆን÷ በዓሉ ሲከበር የተቸገሩ ወገኖቻችን እና ለሀገር ክብር በግዳጅ ላይ ያሉ የጀግናው መከላከያ ሰራዊት አባላትን ቤተሰብ ደጀን መሆናችንን በማስመስከር መሆን አለበት ብለዋል።