የሀገር ውስጥ ዜና

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  በጅግጅጋ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የአስፓልት መንገድ ግንባታ ሥራዎችን ጎበኙ

By Meseret Demissu

January 08, 2022

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ በጅግጅጋ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የአስፓልት መንገዶችን ጎብኝተዋል፡፡

በአቶ ሙስጠፌ የተመራው የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በጅግጅጋ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የመንገድ ልማት ስራዎችን እና ከተማውን ለማስዋብ እየተሰሩ ያሉትን ስራዎች ተዘዋውረው  ጎብኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በጉብኝታቸው በመንገድ መሀል ዛፍ የተከሉ ሲሆን÷  በአጠቃላይ በአስፓልት መንገዱ  ዳርቻ ከ5 ሺህ  በላይ ዛፎች  መጽደቃቸውን ከክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!