አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአማራ እና አፋር ክልሎች በከፈተው ጦርነት ምክንያት በጋሸና ከተማ ለወራት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስጀመር የተማሪዎች ምዝገባ ተጀምሯል::
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጋሸና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተገኝቶ ባደረገው ምልከታ አሸባሪው ቡድን ትምህርት ቤቱን ከህንጻው ውጭ ያሉ ንብረቶችን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ተመልክቷል።