የሀገር ውስጥ ዜና

በደብረ ብርሃን የሚገኙ ፋብሪካዎች መደበኛ የምርት ሂደታቸውን በመቀጠል የውጭ ምንዛሪ እያስገኙ ነው

By Feven Bishaw

January 11, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በህልውና ዘመቻው ወቅት በደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ በማምረቻ ዘርፍ የተሰማሩ ሦስት የውጭ ሀገር አምራች እና አንድ የግል አልሚ ባለሐብቶች ምርቶቻቸውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ገለጹ፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ክትትልና ድጋፍ መምሪያ ሃላፊ ብርሃን አለምነህ በደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ የነበሩ ኩባንያዎች የምርት ሂደታቸውን ሳያስተጓጉሉ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ሲያቀርቡ ነበር ብለዋል።