አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2014፣ (ኤፍ ቢ ሲ) ዳያስፖራውን በቴክኖሎጂ ዘርፍ የቢዝነስ አማራጮች እንዲሰማራና በሀገር ውስጥ ካሉ ባለሙያዎች ጋር እንዲተዋወቅ የሚያደርግ የበይነ መረብ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፥ ዳያስፖራው የውጪ ምንዛሬ በሚያስገኝ፣ ለወጣቶች የስራ እድል በሚፈጥርና የዓለም አቀፉን የገበያ ፍላጎት ታሳቢ ባደረገ ስራ ላይ እንዲሰማራ ጠይቀዋል፡፡