የሀገር ውስጥ ዜና

ዳያስፖራው በቴክኖሎጂ ዘርፍ የዓለም አቀፉን የገበያ ፍላጎት ታሳቢ ባደረገ ስራ ላይ እንዲሰማራ ተጠየቀ

By Feven Bishaw

January 12, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2014፣ (ኤፍ ቢ ሲ) ዳያስፖራውን በቴክኖሎጂ ዘርፍ የቢዝነስ አማራጮች እንዲሰማራና በሀገር ውስጥ ካሉ ባለሙያዎች ጋር እንዲተዋወቅ የሚያደርግ የበይነ መረብ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፥ ዳያስፖራው የውጪ ምንዛሬ በሚያስገኝ፣ ለወጣቶች የስራ እድል በሚፈጥርና የዓለም አቀፉን የገበያ ፍላጎት ታሳቢ ባደረገ ስራ ላይ እንዲሰማራ ጠይቀዋል፡፡