አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥምቀትን በዓልን በጎንደር ከተማ ”የአንድነት ደወል ጥምቀትን በጎንደር” በሚል መሪ ቃል ለማክበር ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ተናገሩ።
ምክትል ከንቲባው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ ከጥር 5 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በከተማዋ ለሚከበረው የጥምቀት በዓል አካል ለሆነው የባህል ሳምንት የተለያዩ ዝግጅቶች ይደረጋሉ፡፡