አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ለምርትና ምርታማነት ወሳኝ ሚና የሚጫወተው የአካባቢ ጥበቃ ስራ ተጀምሯል፡፡
በክልሉ በምዕራብ አርሲ ዞን የ2014 ዓ.ም የተፋሰስ ልማት ስራዎች ዛሬ በሲራሮ ወረዳ የተጀመረ ሲሆን፥ የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር አብዱላሂ ቤካ፥ በዞኑ 13 ወረዳዎች 324 ተፋሰሶች ላይ የተፋሰስ ልማት ስራው እንደሚሰራ ተናግረዋል።