አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ካናዳውያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍ በጎ አድራጎት ድርጅት በአጣዬ ከተማ በአሸባሪዎቹ ሸኔና ህወሃት የወደሙ የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀመጠ።
የከተማዋ አስተዳድር ከንቲባ አሳልፍ ደርቤ እንደተናገሩት፥ በከተማዋ ህወሃትና ሸኔ በጋራ ሆነው 420 መኖሪያ ቤቶችና 50 ግሮሰሪና ሆቴሎችን አውድመዋል፤ ከ250 በላይ ሰዎችንም ገድለዋል።