አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ እስከ ጥር 13 ቀን 2014ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አስታወቀ፡፡
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1265/2014 ማጽደቁ የሚታወስ ሲሆን÷ በዚሁ መሠረት የዕጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ ከታህሳስ 26 እስከ ጥር 6 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡