አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀጣይነት የማይናወጥ የሰላም ሁኔታ ውስጥ ለመግባትና ሀገርን በጠንካራ አለት ላይ ለማቆም ሀገራዊው የምክክር ኮሚሽኑ አስፈላጊ መሆኑ ተገለፀ፡፡
የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያ አቶ ዘላለም ግዛቸው ከፋና ብሮድካስቲንግ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በየጊዜው በምክክር ነገሮችን ከማለፍና የህዝብን መሰረታዊ ፍላጎትና መሻት መሰረት አድርጎ ፖለቲካውን ከመዘወር ይልቅ በግል ፍላጎት ላይ መንተራሱ ብዙ የቤት ስራዎች እንዲከማቹ እንዳደረገው ይናገራሉ፡፡