የሀገር ውስጥ ዜና

የወልድያ ዩኒቨርሲቲን ስራ ለማስጀመር እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

January 16, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው ህወሃት ጉዳት የደረሰበትን ወልድያ ዩኒቨርሲቲ መልሶ በማቋቋም የመማር ማስተማሩን ስራ ለማስጀመር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አበበ ግርማ ገልጹ።

ዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆን ተደርጎ የተደራጀ እንደነበር የገለጹት ዶክተር አበበ÷አሸባሪው ቡድን ወረራ በፈፀመበት ወቅት ማሽኖች፣ የመብራት፣ የውሃና ሌሎችን የተቋሙን ንብረቶችን በማውደም በታሪክ የማይረሳ ጥቁር ጠባሳ የጣለ ነው ብለዋል ፡፡