አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪው የህወሃት ዝርፊያና ውድመት የደረሰበት የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተደረገው ርብርብ ወደ ስራ መመለሱን የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ሰኢድ ገልፀዋል፡፡
ሥራ አስኪያጁ ÷ ሁሉም የሚመለከተው የመንግስት እና የህብረተሰብ አካል በእልህ እና በቁጭት በመስራት ለስራ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ተሟልተውና መሰረተ ልማቶች ተጠግነው ፓርኩ አገልግሎት እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡