አዲስ አበባ ጥር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ነዋሪነታቸው በአሜሪካ የሆኑት ጥንዶች በምዕራብ ደንቢያ ወረዳ የተለያዩ አካባቢዎች በ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ሶሶት ትምህርት ቤቶችና ሌሎች የልማት ስራዎችን አጠናቀው ለህብረተሰቡ አስረከቡ፡፡
በአሜሪካ ሀገር የሚኖሩት አቶ ተስፋዬ አስማማውና ባለቤታቸው ወይዘሮ አስቴር እንዳለ፥ በምዕራብ ደንቢያ ወረዳ የወደቁ ለደረጃ የማይመጥኑ ትምህርት ቤቶችን በማህበራዊ ትስስር ገፅ በምስል ይመለከታሉ።