የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ኦሞ ዞን በግጦሽ መሬት ምክንያት ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በእርቅ ተፈታ

By Feven Bishaw

January 24, 2022

አዲስ አበባ፣ጥር 16፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በደቡብ ኦሞ ዞን በኛንጋቶም፣ ካራ፣ ሐመርና በኮይጉ ህዝቦች መካከል በግጦሽና በእርሻ መሬት ምክንያት ተፈጥሮ የነበረው ግጭት በእርቀ ሰላም መቋጨቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

በደቡብ ኦሞ ዞን በሚገኙ ህዝቦች መካከል ለዓመታት የዘለቀውን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የእርቀ ሰላም ኮንፍራንስ በዛሬው እለት በሐመር ወረዳ ካራዱስ ቀበሌ ተካሂዷል ።