የሀገር ውስጥ ዜና

በሰሜን ሸዋ ዞን በአጣዬ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ

By Feven Bishaw

January 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ ዞን በአጣዬ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ሌሊት ከወልድያ ወደ አዲስ አበባ 22 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ አጣዬ ከተማ ሲደርስ በቦታው ቆሞ ከነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው።