አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማና ዙሪያ ወረዳ 314 ሀሰተኛ የቀበሌ መታወቂያ ለጠላት አሳልፈው ለመስጠት በድብቅ ሲያጓጉዙ የተገኙ የተባሉ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር እየሩስ አስማረ እንደገለጹት÷ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ ጥር 13 ቀን 2014 ዓም በተደረገ ክትትል በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራዝ ከተማ 104 ሀሰተኛ መታወቂያዎችን ይዞ ተገኝቷል።