የሀገር ውስጥ ዜና

ሃሰተኛ መታወቂያ ለጠላት አሳልፈው ለመስጠት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Feven Bishaw

January 25, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎንደር ከተማና ዙሪያ ወረዳ 314 ሀሰተኛ የቀበሌ መታወቂያ ለጠላት አሳልፈው ለመስጠት በድብቅ ሲያጓጉዙ የተገኙ የተባሉ  ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር እየሩስ አስማረ እንደገለጹት÷ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ ጥር 13 ቀን 2014 ዓም በተደረገ ክትትል በጎንደር ዙሪያ ወረዳ እንፍራዝ ከተማ 104 ሀሰተኛ መታወቂያዎችን ይዞ ተገኝቷል።