የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በወርልድ ቪዥንና በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በቅንጅት በ309 ሚሊየን ዶላር ወጪ የሚተገበር ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

By Feven Bishaw

January 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በወርልድ ቪዥን እና በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በቅንጅት በ5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚተገበር ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ።

ፕሮጀክቱ በ309 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀት የሚተገበር ነውም ተብሏል።