አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በድርቅ ምክንያት ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ከ50 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ፡፡
የአስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉጂ ዞን በድርቁ ጉዳት ለደረባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እና በድርቁ ምክንያት እየተጎዱና እየሞቱ ላሉት እንስሳት የሚሆን የሳርና የመኖ እንዲሁም የውሃ ማጠራቀሚያ ሮቶ ድጋፎችን ለዞኑ አስተዳደር አስረክበዋል፡፡