በተመሳሳይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ ከሀንጋሪ አምባሳደር አቲላ ቶማስ ጋር በነፃ የትምህርት ዕድል ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም የሀንጋሪ መንግስት ለኢትዮጵያውያን ይሰጥ የነበረውን የነፃ የትምህርት ዕድል ስምምነት በማስቀጠል የሁለቱን አገራት ወዳጅነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
አምባሳደር አቲላ ቶማስ በበኩላቸው÷ አገራቸው በሁለተኛ ዲግሪ እና በሶስተኛ ዲግሪ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ነፃ የትምህርት ዕድል ከዚህ ቀደሙ በተሻለ ሁኔታ ቁጥሩን በመጨመር እንደምትሰጥ አረጋግጠዋል፡፡
የነፃ የትምህርት እድሉ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም በውይይቱ ተነስቷል።